Thursday, 2 November 2017

የንባብ ዜና


የንባብ ዜና፦ ስለ መጽሐፍ ሽያጭ፣ ንባብ ነክ መርሐ ግብሮችና የውይይት ግብዣዎችን ለአንባቢዎች መረጃ የሚተላለፍበት ነው፡፡


በዚህ ሳምንት አዳዲስ የመጻሕፍት በረከቶች
በዳዊት ደስታ ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል፡፡
1.   የአዳም ረታ ‹‹አፍ›› አዲስ ረዥም ልብ ወለድ መጽሐፍ ለአንባቢያን አቅርቦል፡፡ መጽሐፉ ማክሰኞ 11 ሰዐት በብሔራዊ ቴአትር ይመረቃል፡፡ 254 ገጾች የተቀነበበ ነው፡፡ ዋጋው 80 ብር ለገበያ ቀርቦል፡፡
2.   የዝነኛው ደራሲ ጃክ ሂግኒስ ‹‹ድሪክ ዊዝ ዴቭል›› በተርጎሚ መልዓከ ተሰማ ‹‹ሰዎቹ›› በሚል ርዕስ ወደ አማርኛ ተመልሶ ለንባብ በቃ፡፡ 216 ገጽ ተቀንብቦ በ61 ብር እየተሸጠ ነው፡፡
3.   ‹‹ከዕለታት አንድ ቀን›› የግጥም መጽሐፍ በሳምሶን የተዘጋጀ ሲሆን መጽሐፉ በ91 ገጾች 60 ግጥሞችን ይዞ በ 50 ብር እየተሸጠ ይገኛል፡፡
4.   ‹‹ምሳሌያዊ አነጋገር›› ሥነ ፍቺያዊ ፋይዳና አንድምታ መጽሐፍ በመምህርት ደራሲና ጋዜጠኛ ወይንሸት በየነ የተዘጋጀ 261 ገጾች ይዞ በ91.25 እየተሸጠ ይገኛል፡፡
ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል፡፡
ምንጭ አዲስ አድማስ መጋቢት  8 ቀን 2010 ዓ.ም
በዚህ ሳምንት አዳዲስ የመጻሕፍት በረከቶች
በዳዊት ደስታ ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል፡፡
1.   ‹‹ያልነጋው ቀን›› በገበያ ላይ ዋለ፡፡ መጽሐፉ በሦስት ክፍሎች የተከፈለ ነው፡፡ ‹‹ዘማን››፣ ‹‹ሶላና›› እና ‹‹ሲፋኒ-‹‹የሰላም ከተማ›› በሚሉ ርዕሶች፡፡ በ167 ገፆች ተመጥኖ የቀረበው ‹‹ያልነጋው ቀን›› ለአገር ውስጥ በ60 ብር ለውጭ አገራት በ20 ዶላር ለገበያ ቀርቧል፡፡
2.   ‹‹ማራ›› ልብ ወለድ መጽሐፍ ነገ ይመረቃል፡፡ የደራሲ ሰናይት ፍቃዴ ‹‹ማራ›› የተሰኘ ረዥም ልብ ወለድ መጽሐፍ በቅርስና ጥናት ጥበቃ ባለሥልጣን አዳራሽ፤ የሥነጽሑፍ ባለሙያዎችና ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት ይመረቃል፡፡
ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል፡፡

ምንጭ አዲስ አድማስ ጋዜጣ፣ መጋቢት 15 ቀን 2010 ዓ.ም
በዚህ ሳምንት አዳዲስ የመጻሕፍት በረከቶች
በዳዊት ደስታ ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል፡፡
1.  ‹‹Empire and Revolution in Ethiopia›› በ345 ገጽ የተቀነበበው መጽሐፍ በ142 ብር በ20 ዶላርና በ15 ዩኬ ለገበያ ቀርቦል፡፡
2.  ‹‹ነጻነትን ፍለጋ››በ183 ገጽ የተቀነበበው መጽሐፍ በ91 ብር ከ60 ሳንቲም ለገበያ ቀርቧል፡፡
3.  ‹‹ክልከላ›› ልብወለድ መጽሐፍ በደራሲ ዮርዳኖስ ሽፈራው የተዘጋጀ ሲሆን በ293 ገጽ ተቀንብቦ የቀረበ ሲሆን በ120 ብር ለአንባብያን ቀርቧል፡፡

ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል፡፡
ምንጭ፦ አዲስ አድማስ ጋዜጣ፣ መጋቢት 22 ቀን 2010 ዓ.ም

በዚህ ሳምንት አዳዲስ የመጻሕፍት በረከቶች
በዳዊት ደስታ ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል፡፡
1.  ‹‹መንግሥትና የግለሰብ ነፃነት››
‹‹መንግሥትና የግለሰብ ነፃነት›› መጽሐፍ በገበያ ላይ ዋለ፡፡ በደራሲ መካሻ አበራ የተፃፈው ‹‹መንግሥትና የግለሰብ ነፃነት›› የብአዴን ጽ/ቤት ኃላፊ በሆኑት አቶ አለምነው መኮንን የተፃፈው ‹‹ፖለቲካ፣ ኢኮኖሚና የኢትዮጵያ ህዳሴ›› ለተሰኘው መጽሐፍ ምላሽ የሚሠጥ ነው ተብሏል፡፡ በአምስት ዋና ዋና ምዕራፎች የተከፋፈለው መጽሐፍ በሪበራል ዴሞክራሲና ገበያ አክራሪነት፣ በምዕራባውያን የገበያ አክራሪነትና ሊበራል ዲሞክራሲ የቀረበውን ትችት ዙርያ የሚያጠነጥን ነው፡፡ በ240 ገፅ የተመጠነው መጽሐፍ በ65 ብር እየተሸጠ ነው፡፡
2.  ‹‹ገለዓድ የፍቅር ተራራ››
በደራሲ አለምነህ እንግዳው የተፃፈው ወጥ ልብወለድ የሆነው ‹‹ገለዓድ የፍቅር ተራራ›› መጽሐፍ የሰሞን ጎዝ (የቅዳሴ) ትምህርት ለመማር ከሩቅ ቦታ ወደ ጎንደር በለሳ ቃላይ መድኃኔዓለም ጥንታዊት ቤተክርስቲያን የሄደ የአንድ ወጣት የትምህርት እና የፍቅር ታሪክ የሚያስቃኝ መጽሐፍ ነው፡፡ በ133 ገጽ የተቀነበበው መጽሐፍ በ60 ብር ለገበያ ቀርቦል፡፡
3.  ‹‹ህይወት ምርጫ ነው››
በዶክተር በላይ ደርዛ ‹‹ህይወት ምርጫ ነው›› የተሰኘ መጽሐፍ ነገ ከረፋዱ 4፡00 ጀምሮ በብሔራዊ ቤተ መጻሕፍትና ቤተ መዛግብት ኤጀንሲ አዳራሽ ይመረቃል፡፡
ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል፡፡
ምንጭ፦ አዲስ አድማስ ጋዜጣ፣ ሚያዝያ  13 ቀን 2010 ዓ.ም
በዚህ ሳምንት አዳዲስ የመጻሕፍት በረከቶች
በዳዊት ደስታ ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል፡፡
1.  ‹‹ያላረፉ ነፍሶች››
የደራሲ ቆንጅት ብርሃን 2ኛ ሥራ የሆነው ‹‹ያላረፉ ነፍሶች›› ረጅም ልብወለድ መጽሐፍ ለንባብ በቃ፡፡ በ398 ገፅ የተቀነበበው መጽሐፍ በ182 ብር ከ50 ሳንቲም ለገበያ ቀርቦል፡፡
2.  ‹‹ጎደኝነት››
በብስራ ጴጥሮስ ዩሣ የተዘጋጀው ‹‹ጎደኝነት እና ሌሎች መሳጭ ታሪኮች›› የአጫጭር ታሪኮችና ግጥሞች ስብስብ መጽሐፍ ከትናንት በስቲያ ጀምሮ በገበያ ላይ ዋለ፡፡ በ125 ገጾች የተቀነበበው መጽሐፍ በመልካም ሥነ-ምግባር እና በባህሪ ተሃድሶ ዙርያ የሚያተኩር 72 አጫጭር መሳጭ ታሪኮችና 13 ግጥሞችን ያካተተ ነው፡፡ ዋጋው 71.50 ብር እየተሸጠ ነው፡፡
3.  በ‹‹ተመስገን ገብሬ ሕይወቱና ስራዎቹ›› መጽሐፍ ላይ ነገ ውይይት ይካሄዳል፡፡
ሚዩዚክ ሜይዴይ ከኢትዮጵስ ኮሌጅ ጋር በመተባበር ነገ ከቀኑ 8፡00 ጀምሮ በብሔራዊ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት ኤጄንሲ አዳራሽ ውይይት ይደረጋል፡፡ በእለቱ ለውይይቱ የመነሻ ሃሰብ የሚያቀርቡት የአሀዱ ኤፍኤም ራዲዮ ሥራ አስኪያጅ፣ ደራሲና ጋዜጠኛ አቶ ጥበቡ በለጠ ሲሆኑ በውይይቱ እንድንገኝ ተጋብዘናል፡፡
ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል፡፡
ምንጭ፦ አዲስ አድማስ ጋዜጣ፣ ሚያዝያ  20 ቀን 2010 ዓ.ም

በዚህ ሳምንት አዳዲስ የመጻሕፍት በረከቶች
በዳዊት ደስታ ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል፡፡
1.  ‹‹ኃይሌ ፊዳ እና የግሌ ትዝታ››
በዶ/ር አማረ ተግባሩ የተጻፈው ‹‹‹‹ኃይሌ ፊዳ እና የግሌ ትዝታ›› የተሰኘ መጽሐፍ ለንባብ በቃ፡፡ መጽሐፉ በ1960ዎቹ መጨረሻ በዋናነት በአውሮፓ የኢትዮጵያ ተማሪዎች ንቅናቄ እንዲሁም የመኢሶን መሪ በነበረው ኃይሌ ፊዳ ህይወት፤ ፖለቲካዊ ሚና እንዲሁም አጠቃላይ አብዮታዊ እንቅስቃሴ የሚያስቃኝ መጽሐፍ ነው፡፡ መጽሐፉ 236 ገጾች የተቀነበበው በ111 ብር ከ50 ሳንቲም በገበያ ላይ ውሏል፡፡
2.  ‹‹የኢንተርፕሪነርሽፕ ሀሁ››
በዶ/ር አቡሽ አያሌውና እንድርያስ አራጋው የተጻፈው ‹‹የኢንተርፕሪነርሽፕ ሀሁ›› መጽሐፍ ‹‹የራስህን ቢዝነስ ለመጀመር አሁኑኑ ተነስ›› በሚል ከንግድ ሀሳብ ፈጠራ እስከ ንግድ ሀሳብ እቅድ አነዳደፍ ድረስ በተግባር የተዋቀረ ትምህርት የሚሰጥ መጽሐፍ ነው፡፡ በ330 ገጾች የተቀነበበው መጽሐፍ በ175 ብር በገበያ ውሏል፡፡
ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል፡፡
ምንጭ፦ አዲስ አድማስ ጋዜጣ፣ ሚያዝያ  27 ቀን 2010 ዓ.ም

በዚህ ሳምንት አዳዲስ የመጻሕፍት በረከቶች
በዳዊት ደስታ ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል፡፡
በህክምና ባለሙያው ቸርነት ገብረ ክርስቶስ የተፃፈው በህክምና ላይ የሚያጠነጥንዲባቶየተሰኘ መፅሐፍ ለንባብ በቃ፡፡ መፅሐፉ በዋናነት በህክምናው አለም ያሉ የአካሚና የታካሚ እውነቶችን በስነ ፅሑፍ ለዛ እያዋዛ እውቀትና ግንዛቤ የሚያስጨብጥ ነው ተብሏል፡፡ 371 ገፆች የተቀነበበው መፅሐፉ 160 ብር እና 20 ዶላር

2.  21ኛው /ዘመን መሳፍንትና ኢትዮጵያን እንደ ሀገር የማስቀጠል ፈተናዛሬ ይመረቃል

የእውቁ ፖለቲከኛና መሐንዲስ / ዘለቀ ረዲ፣21ኛው /ዘመን መሳፍንትና ኢትዮጵያን እንደ ሀገር የማስቀጠል ፈተናየተሰኘው መፅሐፍ የፊታችን ሰኞ ከቀኑ 1100 ጀምሮ በዋቢ ሸበሌ ሆቴል ይመረቃል፡፡ በምርቃት ስነ ስርዓቱ ላይ የመፅሐፉ  ዳሰሳ (review) እንዲሁም ከመፅሐፉ የተመረጡ ክፍሎች የሚቀርቡ ሲሆን ውይይትም ይደረጋል ተብሏል፡፡
ምንጭ፦ አዲስ አድማስ ጋዜጣ፣ ግንቦት 4 ቀን 2010 ዓ.ም
በዚህ ሳምንት አዳዲስ የመጻሕፍት በረከቶች
በዳዊት ደስታ ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል፡፡

የአመራር ሳይንስና ጥበብመፅሀፍ ገበያ ላይ ዋለ

 በኮሎኔል ፈቃደ ገብረየሱስ የተሰናዳውና በአመራር ሳይንስና ጥበብ ላይ ሰፊ ትንታኔ የሚሰጠውየአመራር ሳይንስና ጥበብመፅፍ ገበያ ላይ ዋለ፡፡የሁሉን ነገር መውደቅም ሆነ መነሳት የሚወስነው አመራር ነውየሚለው የጆን ማክስዌልን አመራር ተንተርሶና የተለያዩ ውጤታማ ተሞክሮ ያላቸውን አመራሮች ልምድ ቀምሮ የተዘጋጀው መፅሀፉ በተለያዩ የሙያ ዘርፎች አመራር ያለውን ጉልህ ሚና በማስተማር ሰዎች ቢዝነሳቸውን፣ ቤተሰባቸውን እና ተቋማትን እንዴት መምራት እንደሚችሉ ጥበብን ያላብሳል ተብሏል 704 ገፅ የተቀነበበው መፅሀፉ 300 ብር ለገበያ ቀርቧል ደራሲው ከዚህ ቀደምስትራቴጂየተሰኘው የቢዝነስ ስትራቴጂን እውቀት የሚያስጨብጥ መፅሀፍ ለንባብ ማብቃታቸው ይታወሳል፡፡

ደቦለንባብ በቃ

  ከተለያየ የሙያ ዘርፍ የተውጣጡ 60 ነባርና አዳዲስ ፀሐፍት የተሳተፉበትደቦ 60 ደራሲያንየተሰኘ መፅሀፍ ለንባብ በቃ፡፡ በዚህ መፅሀፍ ላይ ደራሲያን፣ ገጣሚያን መምህራን የሙዚቃ ባለሙያዎች፣ ተዋንያን፣ ጋዜጠኞች እና በተለያየ የሙያ ዘርፍ የተሰማሩ ግለሰቦች ያበረከቷቸው ወጎች፣ አርቲክሎች ግጥሞች፣ የፖለቲካ ትንታኔዎችና መሰል ፅሁፎች ተካትተውበታል፡፡ በዛጎል መፃህፍት ተዘጋጅቶ በደራሲ እንዳለ ጌታ ከበደ አርትኦቱ የተሰራለት መፅሀፉ 516 ገፅ ተቀንብቦ 170 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡
ምንጭ፦ አዲስ አድማስ ጋዜጣ
በዚህ ሳምንት አዳዲስ የመጻሕፍት በረከቶች
በዳዊት ደስታ ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል፡፡

የልብ ቃጠሎእናንውዘትነገ ይመረቃሉ

በገጣሚና ደራሲ አበበ ካብ ይመር የተፃፉትንውዘትየግጥም መፅሐፍናየልብ ቃጠሎየአጫጭር ልቦለዶች ሥብስብ ነገ ከቀኑ 330 ጀምሮ በዋቢ ሸበሌ ሆቴል አዳራሽ ይመረቃሉ፡፡ ንውዘት የግጥም መፅሐፍ በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የሚያጠነጥኑ 80 በላይ ግጥሞችን የያዘ ሲሆን 112 ገፅ ተቀንብቦ 50 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡
የልብ ቃጠሎ የተሰኘውም መፅሃፋቸው በማህበራዊ ጉዳዮች ላይ የሚያጠነጥኑ 12 ያህል አጫጭር ልቦለዶችን የያዘ ሲሆን 134 ገፅ ተቀንብቦ 60 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡ በዕለቱ /ፕሮፌሰር ዘሪሁን አስፋውና /ፕሮፌሰር ደረጀ ገብሬ በመፅሐፍቱ ላይ ዳሰሳ እንደሚያቀርቡና አንጋፋና ወጣት ፀሐፍት ስራዎቻቸውን እንደሚያቀርቡ ለማወቅ ተችሏል፡፡

ግርምተ ሳይቴክመፅሐፍ ተመረቀ

በኢቢኤስ ቴሌቪዥንቴክ ቶክበተሰኘው ሾው አስገራሚ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን በማስተዋወቅና በመተንተን የሚታወቀው የሰለሞን ካሳግርምተ ሳይቴክመፅሐፍ ከትንት በስቲያ ከምሽቱ 1200 ጀምሮ በሸራተን ሆቴል ላሊበላ አዳራሽ ተመረቀ፡፡ መፅሐፉ ለኢትዮጵያውን እንዲያገለግል በአማርኛ የተፃፈ ሲሆን፤ የምረቃው ሥነ ስርዓት በሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የተዘጋጀውን የአይሲቲ ኤክስፖ ኢትዮጵያ 2010 የአይሲቲ ሳምንት ምክንያት በማድረግ የተዘጋጀ እንደሆነና በምረቃ ሥነ ስርዓቱ ላይ የሚኒስትሩ የስራ ኃላፊዎች፣ በዘርፉ የተሰማሩ ባለሙያዎችና ተጋባዥ እንግዶች እንደተገኙም ታውቋል፡፡ 
ምንጭ፦ አዲስ አድማስ ጋዜጣ

በዚህ ሳምንት አዳዲስ የመጻሕፍት በረከቶች
በዳዊት ደስታ ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል፡፡

ዕድል ፈንታላይ ውይይት ይካሄዳል

ሚዩዚክ ሜይዴይ ኢትዮጵያ ከኢትዮጵስ ኮሌጅ ጋር በመተባበር፣ ነገ ከቀኑ 800 ጀምሮ በስነ - ፅሑፍ የኖቤል ሽልማት አሸናፊ በሆነው ጀርመናዊው ደራሲ ሔርማን ካርልሔስናርሲስ ኤንድ ጎልድመንድበሚል በተፃፈውና በተርጓሚ ሰላምይሁን ኢዶሳዕድል ፈንታበሚል ወደ አማርኛ በተመለሰው መፅሐፍ ላይ በብሔራዊ ቤተ መፃሕፍትና ቤተ - መዛግብት ኤጀንሲ አዳራሽ ውይይት ያካሂዳል፡፡
ለውይይቱ የመነሻ ሀሳብ የሚያቀርበውየማዕበል ጥንስስእናሰልስቱ ጣዖታትመፃህፍት ደራሲ ያዕቆብ ብርሃኑ ሲሆን መድረኩን የሚመራው የቋንቋ መምህርና የታሪክ ባለሙያ በሆነው ሰለሞን ተሰማ . እንደሆነ አዘጋጁ ገልፆ፤ በውይይቱ ላይ ፍላጎት ያለው እንዲሳተፍ ጥሪ ቀርቧል፡፡
ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል፡፡
በዚህ ሳምንት አዳዲስ የመጻሕፍት በረከቶች
በዳዊት ደስታ ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል፡፡

የሕይወት እምሻውፍቅፋቂሐሙስ ተመረቀ

ፍቅፋቂበሚል ርዕስ የተዘጋጀው የሕይወት እምሻው ሁለተኛ መጽሐፍ ከትላንት በስቲያ ሐሙስ፣ ሐምሌ 5 ቀን 2010 .. በዋቢ ሸበሌ ሆቴል ተመርቋል፡፡ የደራሲዋ ሁለተኛ ሥራ የሆነው ይህ የልቦለዶችና የወጎች ስብስብ መጽሐፍ፤ 220 ገጾች ላይ የተዘራ ሲሆን 38 ዋና ዋና እና 20 መሻገሪያ ትረካዎችን ያካትታል፡፡
ደራሲዋ እንደ በኩር ሥራዋ ሁሉ በአዲሱ መጽሐፏ  ውስጥ በሚገኙ ትረካዎችም የኢትዮጵያዊያንን ፍቅር፣ ባህል፣ ፖለቲካ፣ የዕለት ተዕለት ሕይወት እያነሳች በቅርበትና በኪናዊ ለዛ ትበልታለች፤ እንደ አስገድዶ መድፈርና ድንግልናን የመሳሰሉ ጉዳዮችንም ተጠየቅ ውስጥ ትከታለች፡፡
ሕይወት ከደራሲነትም ባሻገርነቆራ እና ሌሎችም ወጎች ከሕይወት እምሻው ጋርየተሰኘ ከመቶ ሠላሳ ሺህ በላይ ተከታዮች ያሉት የፌስቡክ ገጿ ላይም በቋሚነት በመጻፍ ትታወቃለች፡፡ በመጽሐፍት መልኩ መገለጥን ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ከመጻፍ ጋር በማነጻጸርሁለቱ ፍጹም የተለያዩ ሂደቶች ናቸውየምትለው ደራሲዋ፤ፌስቡክ ላይ መጻፍ ፍጥነት አለው፤ ስሜታዊና ቅጽበታዊም ነው፡፡ በአብዛኛው በጥሞና ከማሰላሰልና የፈጠራ ችሎታን ከመጠቀም የሚያቅብ ድርጊትም ሊሆን ይችላል፡፡ በአንጻሩ መጽሐፍ ማዘጋጀት ጊዜ ይወስዳል፣ ከፍተኛ ጥንቃቄና ተደራራቢ የአርትዖት ደረጃዎችንም ያልፋልትላለች፡፡
ከሦስት ዓመታት በፊት ባሳተመችው የመጀመሪያ መጽሐፏባርቾየወጎችና የልቦለዶች ስብስብ፣ ኢትዮጵያዊያን ሊነጋገሩባቸው የማይደፍሯቸውንአይነኬጉዳዮች እያነሳች በዋዛና በቁምነገር በመተረኳ የበርካታ አንባቢዎች ልብ ውስጥ እንድትገባ አድርጓታል፡፡
ደራሲዋ ለወደፊትስ እጅሽ ከምን ለሚሏት ወዳጆቿ፤አንድ ረጅም ልቦለድ እየጻፍኩ ነውትላለች፡፡እኔ የምታወቀው ! በሚያደርጉ በጣም አጫጭር ሥራዎች ስለሆነ ይሄ ከዚህ በፊት ያልታየሁበት ቀጠና ይሆናል፡፡ ባርቾእና ፍቅፋቂጋር በይዘትና በቅርጽ የሚመሳሰል ሌላ ሦስተኛ መጽሐፍም አዘጋጃለሁስትልም አክላለች፡፡
ፍቅፋቂበሊትማን መጻሕፍት አከፋፋይነት ካለፈው ሐሙስ ጀምሮ 92 ብር ዋጋ በገበያ ላይ ውሏል፡፡
ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል፡፡
በዚህ ሳምንት አዳዲስ የመጻሕፍት በረከቶች
                በዳዊት ደስታ ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል፡፡

መወልወያ አዟሪው እና ሌሎችምለንባብ በቃ

በደራሲ ሳምሶን ከፍያለው የተደረሱ አምስት አጫጭር ልቦለድ ታሪኮችን ያካተተውመወልወያ አዟሪው እና ሌሎችምመፅሐፍ ገበያ ላይ ዋለ፡፡ መፅሐፉፍቅርና ንፋስ፣ጠርጣራው ደምሴዣንጥላው ስር ሆነንልጅኮነሽእናመወልወያ አዟሪውየተሰኙ ከዕለት ተዕለት ህይወታችን ጋር የተቆራኙ ማህበራዊ ጉዳዮች የተዳሰሱባቸው ታሪኮች ተካትተውበታል፡፡
የደራሲው ሶስተኛ ስራ የሆነው ይሄው መፅሐፍ፤ 140 ገፆች ተቀንብቦ፣ 70 ብር ለገበያ የቀረበ ሲሆን ደራሲው ከዚህ ቀደምእንባና ትውስታእናከእለታት አንድ ቀንየተሰኙ የአጭር ልቦለድና የግጥም መፅሐፎችን ለንባብ ማብቃቱ አይዘነጋም፡፡
ምንጭ፦ አዲስ አድማስ ጋዜጣ
በዚህ ሳምንት አዳዲስ የመጻሕፍት በረከቶች
በዳዊት ደስታ ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል፡፡
የዳንኤል ክብረትየአዲስ አበባ ውሾች
 “-- አሪፍ ውሻ ማለት ክፉ ውሻ ነው፣ እንደ ማለት ነው፡፡ አንተ ክፉ ውሻ ከሆንክ ለጌቶችህ አሪፍ ውሻ ነህ፡፡ ትናከስላቸዋለህ፣ ትጮህላቸዋለህ፣ መንገድ አላፊውን ታስደነብርላቸዋለህ፣ ታስፈራራላቸዋለህ። ለሌላው ክፉ ስትሆን ለጌቶችህ ምርጥ ውሻ ትሆናለህ። በኋላ ላይ ግን እዳው አንተ ላይ ይወድቃል፤ በመጨረሻ አንተው ትወረወራለህ፤ ለጅቦቹም ተላልፈህ ትሰጣለህ-”
ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ከላይ እንዳነበባችሁት ስለየአዲስ አበባ ውሾችያወጋናል- በአዲሱ መፅሐፉ። የአዲስ አበባ ውሾች ግን ተምሳሌታዊ ናቸው - ደራሲው የቀረፃቸው ሰውን እንዲወክሉለት ነው፡፡ ታሪኩ የፖለቲካና ማህበራዊ ስላቅ ሊባል ይችላል። ስለ ዘመኑ ሙሰኛ የመንግስት ባለሥልጣናት፣ ስለ ሞሳኝ ባለፀጎች፣ ስለ ዳያስፖራ ወዘተከጭቁኑ የአዲሳቤ ነዋሪ ጋር እየተነፃፀረ ይተረክልናል - በማራኪ ቋንቋና በሚያዝናና አቀራረብ፡፡ 253 ገፆች የተቀነበበው የዳንኤል ክብረት መፅሐፍ፤ 100 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡
በዚህ ሳምንት አዳዲስ የመጻሕፍት በረከቶች
በዳዊት ደስታ ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል፡፡

ሌላ ዓለምየአጫጭር ልቦለዶች መጽሐፍ

በተለያዩ ጭብጦች ላይ የሚያጠነጥኑ 18 አጫጭር ልቦለዶችን ያካተተው የደራሲ ዮናስ ብርሃኔሌላ ዓለምየተሰኘ መፅሐፍ ለንባብ ቀረበ፡፡ 132 ገፆች የተቀነበበው መፅሐፉ፤ 65 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡ ደራሲ ዮናስ ብርሃኔ ከዚህ ቀደምአማሌሌ እና ሌሎችምበተሰኘ መፅሐፍ ውስጥ ሁለት ወጎችንና ሁለት አጫጭር ልቦለድ ታሪኮችን በማዋጣት ለንባብ ያበቃ ሲሆን አዲስ አድማስን ጨምሮ በተለያዩ ጋዜጦችና መፅሔቶች ላይ በሚያቀርባቸው ፅሑፎች ይታወቃል፡፡
በዚህ ሳምንት አዳዲስ የመጻሕፍት በረከቶች
በዳዊት ደስታ ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል፡፡

መቆያ 1” እናእሪ በከንቱየግጥም መድበሎች

በገጣሚ መላዕከ ብርሃን አድማሱ የተፃፉና በበርካታ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ 110 በላይ ግጥሞችን ያካተተውመቆያ 1” የግጥም መድበል በገበያ ላይ ዋለ፡፡ 121 ገፆች የተመጠነው መፅሐፉ፤ 100 ብር ለገበያ የቀረበ ሲሆን በቅርቡ እንደሚመረቅም ተነግሯል፡፡
በተመሳሳይ፤ በአዲስ አበባ በልማት ስም እየተነሱ ወደ ጥግ በሚገፉ ነዋሪዎችና በመዲናዋ መቆሸሽ ዙሪያ የሚያጠነጥኑ 80 በላይ ግጥሞችን የያዘውእሪ በከንቱየተሰኘው የገጣሚ ዳንኤል ታረቀኝ የግጥም መድበል ሰሞኑን ለንባብ በቅቷል፡፡
 ሪፖርተርጋዜጠኛ ነአምን አሸናፊ በመፅሐፉ ጀርባ ላይ ባሰፈረው አስተያየት፤ “… በዚህ የግጥም መድበል ውስጥ ለአብነት ያህልጮኸብኝ ዝምታየኛ ቤትሽንትና አዲስ አበባዝምታ መልስ ነውወዴት አለሽ ሞራልጉዞ ወደ ሁካታእናየደም ውለታየተሰኙት ስነ ልቦናዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ግጥሞች የገጣሚውን ጥልቅ ትዝብት ያንፀባርቃሉ፡፡ብሏል፡፡ 84 ገፆች ያሉት መድበሉ፤ ዋጋው 46 ብር 90 ሳንቲም ነው፡፡
በዚህ ሳምንት አዳዲስ የመጻሕፍት በረከቶች
በዳዊት ደስታ ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል፡፡

ከትግል ትዝታዎቼመፅሐፍ

 በአንጋፋው የህወሓት ታጋይና መስራች ግደይ ዘርአጽዮን የተፃፈውከግል ትዝታዎቼየተሰኘ መፅሐፍ ገበያ ላይ ውሏል፡፡ ታጋዩ ጸሃፊ፤ በሴረኞች ተቀጨ የሚሉትን የደደቢት አብዮት በስፋት በሚተረኩበት በዚህ መጽሐፋቸው፤ህወሓትን አስመልክቶ በጭፍን ጥላቻ ስለተፃፉ መፅሐፍትና በህወሓት ውስጥ ያልሰሩትን ሰሩ ብሎ ግለሰቦችን በማሞገስ ህዝቡ የአምልኮ ያህል እንዲቀበላቸው የተደረገበትን መንገድ ያጋልጣሉ፡፡ ስለ ድርጅቱ በመጠኑም ቢሆን በሚዛናዊነት የጻፉ ግለሰቦችን የሚጠቅሱት የህወኃት መሥራች፤ሁሉም ፀሐፍት ለአሁኑ መፅሐፋቸው መነሻ በመሆናቸው አመስግነዋል፡፡
ከድርጅቱ እስከለቀቁበት ጊዜ ድረስ በከፍተኛ የአመራር ቦታ ላይ እንደነበሩ በመግለፅም፤ ትክክለኛውን የህወሓትን መልክና ቁመና በትክክለኛው መንገድ ለማሳየት ጥረት ማድረጋቸውን ጠቁመዋል፡፡ የተለያዩ ሰነዶችንና ምስሎችን ጨምሮ 261 ገፆች የተቀነበበው መፅሐፉ፤ 200 ብር ለገበያ የቀረበ ሲሆን ክብሩ መፅሐፍት መደብር እያከፋፈለው መሆኑ ታውቋል፡፡
ምንጭ፦ አዲስ አድማስ ጋዜጣ
በዚህ ሳምንት አዳዲስ የመጻሕፍት በረከቶች
በዳዊት ደስታ ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል፡፡

ምስጢረ ፊደልለገበያ ቀረበ

ደራሲ፣ ጋዜጠኛና የባህል ተመራማሪ መምህር ካሕሳይ /እግዚአብሔር ያዘጋጁትምስጢረ ፊደል ወትርጓሜሁ” (የፊደል ምስጢር ከእነ ትርጉሙ) የተሰኘ መፅሐፍ ሰሞኑን ለገበያ ቀረበ፡፡
ምስጢረ ፊደል፤ የግዕዝ ቋንቋና ፊደል ለሀገራችን ሥነ ፅሁፍ ባህል፣ ትውፊትና ታሪክ መሰረትና ምንጭ ብቻ ሳይሆን የጥንታዊ ሥልጣኔያችን መሰረትእንዲሁም የግዕዝ ፊደል የራሱ ትርጉምና ምስጢር ያለው መሆኑን የሚያሳይና በውስጡ ለጥናትና ምርምር መነሻ የሚሆኑ አዳዲስ መረጃዎችን ያካተተ ነው፡፡ ከሁሉም በላይ በትክክለኛ የሆሄያት አፃፃፍ መሰረት መፃፍ ለሚፈልጉ ፀሐፍት፣ ደራሲያን፣ ተማሪዎች በመረጃ ምንጭነት የሚያገለግል ጭምር ነውብለዋል ደራሲው - ስለ መፅሐፉ በላኩት አጭር ሃተታ፡፡ምስጢረ ፊደልለደራሲ ካሕሳይ ሰባተኛ መፅሐፋቸው ሲሆን ከዚህ ቀደምየኃብር ብዕር መፅሐፍ” (1 መፅሐፍ እስከ 3 መፅሐፍ)ምንኩሳን በኢትዮጵያብፅዓን እነማን ናቸውእናባህልና ክርስቲያናዊ ትውፊት በኢትዮጵያየሚሉ መፃህፍትን ለንባብ ማብቃታቸው ይታወሳል፡፡ 292 ገፆች የተቀነበበውምሥጢረ ፊደል 110 ብር ይሸጣል፡፡
ምንጭ፦ አዲስ አድማስ ጋዜጣ
በዚህ ሳምንት አዳዲስ የመጻሕፍት በረከቶች
በዳዊት ደስታ ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል፡፡
የቀድሞ የመንግሥት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ሚኒስትር ዴኤታ የነበሩትና በአሁኑ ወቅት ኢሳትፖለቲካዊ ጉዳዮች ተንታኝና ፕሮግራም አዘጋጅ በሆኑት አቶ ኤርሚያስ ለገሰ የተጻፈውጥላሁን ያረፈ ቀንየተሰኘ መጽሐፍ በሳምንቱ መገባደጃ ላይ ለአንባቢያን ቀርቧል፡፡
310 ገፆች የተቀነበበው መፅሐፉ፤ 182 ብር ለገበያ የቀረበ ሲሆን ከመፅሐፉ ገቢ ግማሹ፣ ለበርካታ ዓመታት በእስር ለቆየው ፖለቲከኛ ክንፈ ሚካኤል ደበበ (አበበ ቀስቶ) የህክምና ወጪ እንደሚውል ለማወቅ ተችሏል፡፡ ደራሲው የመፅሐፉን መታሰቢያነት ለክቡር ዶክተር አርቲስት ጥላሁን ገሰሰ አድርጓል፡፡ አቶ ኤርሚያስ ለገሰ፤ ከዚህ ቀደምባለቤት አልባ ከተማእናየመለስ ልቃቂትየተሰኙ አገራዊ የፖለቲካ ጉዳዮችን የሚዳስሱ መጻሕፍትን ለአንባቢያን ማድረሳቸው ይታወሳል፡፡ 

ለኢትዮጵያ አንድነት የተከፈለ የደምና የአጥንት ዋጋ

  በደራሲ ደርቤ መንግስቱ የተፃፈውና በወቅቱ የአገሪቱ የለውጥ ሂደት ላይ የሚያጠነጥነውለኢትዮጵያ አንድነት የተከፈለ የደምና የአጥንት ዋጋየተሰኘ መጽሐፍ ሰሞኑን ለንባብ በቅቷል፡፡
መፅሐፉ 20 አመታት መለያየት በኋላ በወረደው ሰላም ዳግም ስለተገናኙት የኢትዮጵያና ኤርትራ ህዝቦች፣ ባልተፈፀመ ታሪክ ጥላቻን በመንዛት፣ በአማራና ኦሮሞ ወንድማማች ህዝቦች ላይ ተፈጥሮ ስለነበረው ግጭትና ግጭቱ ስለተፈታበት መንገድ እንዲሁም ለአገር አንድነት ሲባል ስለተከፈለ መስዋዕትነት በጥልቀት ይዳስሳል። ለአገራቸው ደምና አጥንት የከፈሉ ጀግኖችን ክብርና ሞገስ የሚሰጠው መጽሐፉ፤አንዳንዶቹን በፎቶግራፍ ጭምር በማስደገፍ ለመዘከር ይሞክራል፡፡ መጽሐፉ 291 ገጾች የተቀነበበ ሲሆን 160 ብር ይሸጣል፡፡
በደራሲ አበበ ኃብተሥላሴ የተጻፈውና አዲሱ የለውጥ ጉዞን አቅጣጫ የሚያመላክተውኢትዮጵያዊነት፣ ኢኮኖሚያዊ ልማትና እንቆቅልሾቹየተሰኘ መፅሐፍ ገበያ ላይ ዋለ፡፡
መፅሐፉን ለመፃፍ ያነሳሳቸው፣ በምርጫ 97 የተፈፀመው የህዝብየሚመራኝን እመርጣለሁእና የአገዛዙ የድምፅ መስረቅና የህዝብን ድል የመቀልበስ ድርጊት እንደሆነ በመግቢያቸው የጠቆሙት ደራሲው፤ በወቅቱ ስለ ህወሓት/ኢህአዴግ ልማታዊ መንግስትነት የቀረቡ ፅሁፎች ህዝብን የተሳሳተ እሳቤ እንዲይዝ ያደረገ በመሆኑ፣ ይህንን የተሳሳተ እሳቤ ለማስተካከልና በዘርፉ የተሰማሩ ባለሙያዎች፣ ተጨማሪ ፅሁፍ እንዲያቀርቡ ለማነሳሳት መሆኑን ያስረዳሉ፡፡ ስለ ስልጣኔ አካሄድ በኢትዮጵያ፣ ስለ ኢኮኖሚያዊ ዕድገትና ኢኮኖሚያዊ ልማት፣ ስለ ልማታዊ መንግስትና ምንነትና ተያያዥ ጉዳዮች በስፋት የሚዳስሰው መፅሐፉ፤ በአራት ክፍሎች፣ በሰባት ምዕራፎችና 216 ገፆች የተቀነበበ ሲሆን 100 ብር እና 20 ዶላር ለገበያ ቀርቧል፡፡ መጽሐፉን ክብሩ መፅሐፍት መደብር እንደሚያከፋፍለው ለማወቅ ተችሏል፡፡
ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል፡፡
ምንጭ፦ አዲስ አድማስ ጋዜጣ
በዚህ ሳምንት አዳዲስ የመጻሕፍት በረከቶች
በዳዊት ደስታ ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል፡፡

የጨለማው መጋረጃ ሲቀደድነገ ይመረቃል

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
 በደራሲ ሳህሉ አድማሱ የተዘጋጀውየጨለማው መጋረጃ ሲቀደድየተሰኘ መፅሐፍ ነገ ከቀኑ 800 ጀምሮ ቤሊየር አካባቢ በሚገኘው አዲስ ቪው ኢንተርናሽናል ሆቴል ይመረቃል፡፡ የምረቃ ሥነ ስርዓቱ በተለያዩ ኪነ ጥበባዊ ዝግጅቶች የሚታጀብ ሲሆን መፅሐፉም ይገመገማል ተብሏል፡፡መፅሐፉ /ሚኒስትር / ዐቢይ አህመድ ወደ ስልጣን ከመጡ ወዲህ በሳቸው አመራር የተመዘገቡ ዋና ዋና አስደማሚ ለውጦችን የሰነደ ሲሆን /ሚኒስትሩ ያደረጓቸውን ንግግሮችና ያስተላለፏቸውን መልዕክቶችም ያካተተ መሆኑ ታውቋል፡፡ የመፅሐፉም ዋና ዓላማ፤ቀጣዩ ትውልድ የመደመርን ሥርዓት፣ የይቅርታንና የፍቅርን ባህል ጠንቅቆ እንዲያውቅና በተግባር ላይ እንዲያውለው፣ኢትዮጵያዊነትን እንዲለማመድ ማድረግ ነውይላል - በመጽሐፉ ላይ የሰፈረው ማስታወሻ፡፡ 108 ገፆች የተቀነበበው መፅሐፉ፤ 80 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡
ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል፡፡
ምንጭ፦ አዲስ አድማስ ጋዜጣ

የማስጠንቀቂያ ደወልላይ ነገ ውይይት ይካሄዳል

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
ሚዩዚክ ሜይዴይ ኢትዮጵያ ከኢትዮጵስ ኮሌጅ ጋር በመተባበር ነገ ከቀኑ 800 ጀምሮ በአርክቴክት ሚካኤል ሽፈራውየማስጠንቀቂያ ደወልመፅሐፍላይ በብሔራዊ ቤተ መፃህፍትና ቤተ መዛግብት ኤጀንሲ አዳራሽ ውይይት ያካሂዳል፡፡ለውይይቱ የመነሻ ሀሳብ የሚያቀርቡት በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የገቨርናንስና ዴቨሎፕመንት ትምህርት ክፍል መምህር ሲሆኑ መድረኩን የሚመሩት አቶ ሰለሞን ተሰማ ናቸው ተብሏል።ፍላጎት ያለው በውይይቱ ላይ እንዲሳተፍ ሚዩዚክ ሜይዴይ ጋብዟል፡፡
ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል፡፡
ምንጭ፦ አዲስ አድማስ ጋዜጣ

 

No comments:

Post a Comment